ተዐምረኛው መልዐክ ፈታሔ ማሕፀን ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሩፋኤል
ከጌቴ ገሞራ ዘዋድላ ወዘዋሸራ አምጻኤ ዓለማት ገባሬ መላዕክት ልዑል እግዚአብሔር ቅዱሳን መላዕክትን በነገድ መቶ በከተማ ዐሥር አድርጎ ፈጥሯቸዋል ፡፡ የእሊኽ ቅዱሳን መላዕክት ተፈጥሮ ዋነኛ ዓላማም እርሱ ፈጣሪያቸው ሕያው እግዚአብሔርን ያመስግኑ ዘንድ ሲኾን ዳግመኛም ስለፍጥረተ ዓለም ኹሉ መዳንና ይለምኑ ዘንድ ነው ፡፡ ኢሳ = 6÷3 ፡፡ ሪእ 5÷11 ፡፡ ዕብ = 1÷14 ፡፡ ማቴ = 8÷10 ፡፡…