መግቢያ

ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ሰማዕት ዘእንበለ ደም አለቃ አያሌው ታምሩ ፲፱፻፹ወ፰ (1988) ዓመተ ምሕረት እስከ ፲፱፻፺ወ፱ (1999) ዓመተ ምሕረት ድረስ በመኖሪያ ቤታቸው እየተገኙ ለሚማሩ ተማሪ ዎቻቸው በእየሳምንቱ ቅዳሜ የሚያስተምሯቸውን ትምህርታተ ቃለ እግዚአብሔር በእየጊዜው በራሱ መቅርፀ ድምፅ (ቴፕሪከርደር) እየቀረፀ ያሰባስብ የነበረው ከብላቴንነቱ ጀምሮ ደቀ መዝሙራቸው የኾነው ሣሙኤል ኃይሉ በኹለት ሺኅ ዓመተ ምሕረት እንድማርባቸውና መንፈሳዊ ዕውቀት እንዳገኝባቸው ሰጥቶኝ ስማርባቸው ቆይቻለሁ ፡፡

     የሀገራችን ኢትዮጵያ ብቸኛ ሀብቶች የኾኑ ስለቤተ ክርስቲያን እምነትና ትምህርት ሥርዓትም ስለሃይማኖትና ባህል ዘመን አቈጣጠ ርና ሰንደቅ ዓላማ ታሪክና ቋንቋ ስለፊደልና ትውፊት ስለሥርዐተ አስተዳደርና ስለመሳሳሉት ጉዳዮች የተላለፉ የሊቁ መምህራችን አለቃ አያሌው ታምሩ ትምህርቶች ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን በነፃ እንዲ ዳረስ በማሰብ በ www.Danielgebremeskel.com ድህረ ገጽ የለቀቅኹት (የሚገኝ) ሲኾን አርእስቱም የሚከተሉት ናቸው ፡፡

 

ክቡራን ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ሆይ ለድምጹ ጥራት ይቅርታ እየጠየኩ በዚህ አጋጣሚ የድምፅ ባለሙያ የሆናችሁ የድምጹን ጥራት በማስተካከል መንፈሳዊ በረከት እንድትሳተፉ በአክብሮት ጥሪዬን አቀርባለሁ::

እነዚህን ጽሑፎች የጻፉት ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የቤተክርስቲያናችን የቅኔ ሊቅ ናቸው አስፈላጊ በኾነ ጊዜ ስማቸውን እንጠቅሳለን ለጊዜው ግን በብዕር ስማቸው “ጌቴ ገሞራው”በሚለው ይጽፋሉ

ትምህርት ተ.ቁ. 01 እስከ 15

ትምህርት ተ.ቁ. 16 እስከ 30

ትምህርት ተ.ቁ. 31 እስከ 45

ትምህርት ተ.ቁ. 46 እስከ 60

ትምህርት ተ.ቁ. 61 እስከ 80

ትምህርት ተ.ቁ. 81 እስከ 100

ትምህርት ተ.ቁ. 101 እስከ 122

ትምህርት ተ.ቁ. 123 እስከ 140

ትምህርት ተ.ቁ. 141 እስከ 150

2 thoughts on “የአለቃ አያሌው ታምሩ ትምህርቶች

  1. እግዚአብሔር ይባርክህ! ታላቅ ሥራ ነው። ለማመስገን ቃላት የለኝም።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *